“ድምጽ ነኝ!”

  • Read 28070 times
  • Print
  • Email

“አንተ ማን ነህ?” ቢሉት ማዕረጉን ፍለጋ

 ሰባኪዉ ዝም ጭጭ መልስ የለም እርሱ ጋ

“በል ባክህ ንገረን

ደግሞ እንቸኩላለን

ለሚጠባበቁን ወሬ እናደርሳለን፤

እንዲህ የሆነ እንደሁ ዝናህም ይወጣል

አገር ጉድ እያለ በክብር ያጅብሃል።”

ጠብ የሚል ሲጠፋ የሚደረድረዉ

የማዕረግ አይነት የሚከናነበዉ

እንደነበር ሲቆም በአንክሮ እያያቸዉ

አማራጭን ሰጡት እንዲመርጥላቸዉ።

“ክርስቶስ ነህ ኤልያስ ወይስ ነቢዩ ነህ? 

ምንስ ነዉ ማዕረግህ ማን ብለን እንጥራህ?

እባክህ ንገረን  ክብር  ደረጃህን

ስምና መለያ የሚመጥንህን”

ያን ጊዜ ከበደዉ መታገስ አቃተዉ

ማድመጥም አልቻለ እንኳን ሊደርበዉ

የሚጯጯሁትን ቀና ብሎ አየና

“ድምጽ ነኝ”! አላቸዉ እጅጉን ጮኸና

ያመጡትን ኮከብ የሚለጥፉትን

አራግፎ ከላዩ ሰዉ ሠራሽ ማዕረግን 

እንዲህ ሲል ቀጠለ ሰባኪው ጩኸቱን፡-

“ድምጽ ነኝ፣ ድምጽ ነኝ ያዉም የበረሀ

መንገድ የሚያቀና እንዲያልፍበት ዉሀ

እንደልቡ እንዲሔድ ሕይወት ሰጭዉ ጅረት 

ጥርጊያዉን አቅኝ ነኝ በሚሰጠኝ ምህረት 

በሉ አትነዝንዙኝ ማንነቴ ይህ ነው

ሌላ ምንም የለኝ ስለራሴ እምለዉ

ኋላዬ ያለዉ ግን ባለማዕረግ ነዉ

ከሰማይ የመጣዉ ክርስቶስ ጌታዬ 

ከሁሉ በላይ ነዉ።”

 

 (ዮሐ 1፧19-28)

 

 

Last modified onTuesday, 21 April 2015 10:05
Mamusha Fenta

Mamusha Fenta is a Bible expositor and conference speaker residing in Addis Ababa, Ethiopia.

Website: www.mamushafenta.com/

2 comments

  • Kumeneger
    Kumeneger Friday, 01 May 2015 17:44 Comment Link

    I just say waw...... it's well said in a poem and I pause a lit bit and thinking about my self and my people, we almost cover the name of the mighty God with our worthless story. what a disaster??
    Dear brother Mamusha, May God give you more courage and grace to write and teach.

  • Selam
    Selam Wednesday, 22 April 2015 21:24 Comment Link

    It was an amazing poem Mamusha! Thanks for sharing.

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

Log in or Sign up