Logo
Print this page

“ድምጽ ነኝ!”

“ድምጽ ነኝ!”

“አንተ ማን ነህ?” ቢሉት ማዕረጉን ፍለጋ

 ሰባኪዉ ዝም ጭጭ መልስ የለም እርሱ ጋ

“በል ባክህ ንገረን

ደግሞ እንቸኩላለን

ለሚጠባበቁን ወሬ እናደርሳለን፤

እንዲህ የሆነ እንደሁ ዝናህም ይወጣል

አገር ጉድ እያለ በክብር ያጅብሃል።”

ጠብ የሚል ሲጠፋ የሚደረድረዉ

የማዕረግ አይነት የሚከናነበዉ

እንደነበር ሲቆም በአንክሮ እያያቸዉ

አማራጭን ሰጡት እንዲመርጥላቸዉ።

“ክርስቶስ ነህ ኤልያስ ወይስ ነቢዩ ነህ? 

ምንስ ነዉ ማዕረግህ ማን ብለን እንጥራህ?

እባክህ ንገረን  ክብር  ደረጃህን

ስምና መለያ የሚመጥንህን”

ያን ጊዜ ከበደዉ መታገስ አቃተዉ

ማድመጥም አልቻለ እንኳን ሊደርበዉ

የሚጯጯሁትን ቀና ብሎ አየና

“ድምጽ ነኝ”! አላቸዉ እጅጉን ጮኸና

ያመጡትን ኮከብ የሚለጥፉትን

አራግፎ ከላዩ ሰዉ ሠራሽ ማዕረግን 

እንዲህ ሲል ቀጠለ ሰባኪው ጩኸቱን፡-

“ድምጽ ነኝ፣ ድምጽ ነኝ ያዉም የበረሀ

መንገድ የሚያቀና እንዲያልፍበት ዉሀ

እንደልቡ እንዲሔድ ሕይወት ሰጭዉ ጅረት 

ጥርጊያዉን አቅኝ ነኝ በሚሰጠኝ ምህረት 

በሉ አትነዝንዙኝ ማንነቴ ይህ ነው

ሌላ ምንም የለኝ ስለራሴ እምለዉ

ኋላዬ ያለዉ ግን ባለማዕረግ ነዉ

ከሰማይ የመጣዉ ክርስቶስ ጌታዬ 

ከሁሉ በላይ ነዉ።”

 

 (ዮሐ 1፧19-28)

 

 

Last modified onTuesday, 21 April 2015 10:05
Mamusha Fenta

Mamusha Fenta is a Bible expositor and conference speaker residing in Addis Ababa, Ethiopia.

Website: www.mamushafenta.com/
mamushafenta.com © All rights reserved. Website Design @ BEKI Square