Super User

Super User

Equip Media App Launched

We are happy to introduce to you our new app we just launched- it's called "Equip Media".  Through this app you will now be able to get our sermons in video and audio as well as read our articles right on your phone or tablet.  You can download "Equip Media" on all Apple and Android devices.  Just search for "Equip Media" or "Mamusha Fenta" in your app store.  It's easy !

Equipping people with God's word!

Read more...

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ጠቅላላ ጉባኤ

ጉባኤው የተካሔደው ከሚያዚያ 20-22 2007 ሲሆን ከመላው አገሪቱ አባል አብያተ ክርስቲያናትና ድርጅቶችን የወከሉ መሪዎች ተገኝተው ነበር። የጉባኤው መሪ ጥቅስ “ዘመናችንን እንደቀድሞ አድስ” (ሰቆ ኤር 5፡21) የሚል ሲሆን በሦስቱ ቀናት የጉባኤው የማለዳ ክፍለ ጊዜያት የጌታን ቃል በተከታታይ የማካፈሉ እድል ለወንድም ማሙሻ ተሰጥቶት ነበር።

በነዚሁ ቀናት “የቀድሞ ፍቅርን ስለ ማደስ” በሚል ርእስ ለጉባኤው መልእክት ቀርቧል። እግዚአብሔር የጠራን ‘ሙያተኛ አገልጋዮች’ እንድንሆን ሳይሆን አፍቃሪዎቹ እንድንሆን ነው። አገልግሎትና መሪነትም የፍቅር ምላሽ እንጂ የፍቅር ምትክ ሊሆኑ አይገባም። ጌታችን ለሎዶቂያ ቤ/ክ እንዳስጠነቀቀው ለብ ባለ ፍቅር ከኖርን የመተፋት እጣ ይጠብቀናል።

በመሆኑም ልባችንን መክፈትና ከእርሱ ጋር ሕብረትን በማድረግ ፍቅራችንን ማደስ ያስፈልገናል። እግዚአብሔር የሚያድስ አምላክ ነው። መመለስና ፊቱን መፈለግ ግን ይጠበቅብናል። የሚመጡት ዓመታት የቤተክርስቲያን የተሃድሶ ዓመታት ይሆኑ ዘንድ ከመሪዎች ብዙ ይጠበቃል። በጸሎትና በጾም ወደ ሕልውናው፣ ወደ ቃሉና ወደ መስቀሉ ሥራ መመለስ ያስፈልጋል የሚሉትና ሌሎች ተጨማሪ ትምህርቶች በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ቀርበዋል።

ተሳታፊ መሪዎችም በምልጃ ጸሎት ለመልእክቱ የሚገባውን ምላሽ ሰጥተዋል። 

እግዚአብሔር በነገር ሁሉ ይክበር!

Read more...
Subscribe to this RSS feed

Log in or Sign up