የመስቀሉ መንገድ

  • Read 11676 times
  • Print
  • Email

እግዚአብሔር “የአሠራር ማሻሻያ” የሚለባል ነገር እንደማያደርግ ታውቃላችሁ? በጥንቱ መሠረት ነዉ አዳዲስ ነገሮችን የሚያደርገዉ እንጅ መሥሪያ መርሁ እንዳይሻሻል አድርጎ ጨክኗል!

የአዲስ ኪዳን ገጾች በደንብ እንደሚያስረዱን እግዚአብሔር ሊሠራ የመረጠዉ መንገድ እንደሰዉ ጥበብ “ሞኝነት” በሚመስለዉ በመስቀሉ መንገድ ብቻ ነዉ። ለምሳሌ እግዚአብሔር የሚያድነዉ፣ ሐጢያተኞች የመስቀሉን ቃል አምነዉና ተቀብለዉ በእርሱ መንገድ ሲመጡ ብቻ ነዉ (“የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነዉ” 1ቆሮ 1፡18፣ “ዓለም እግዚአብሔርነ በጥበቧ ስላላወቀች በስብከት ሞኝነት የሚያምኑትን ሊያድን የእግዚአብሔር በጎ ፈቃድ ሆኖአልና” ቁ.21) ። ይህ ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔር የመንፈሱን ጉልበትና ቅባት የሚገልጠዉና የሚሠራዉ በመስቀሉ መርህ ብቻ ነዉ (“በመካከላችሁ ሳለሁ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ ነገር እንዳላዉቅ ይህን ቆርጨ ነበርና።…ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበር… 2ቆሮ 2፡1-5)

ይህ የመስቀሉ መንገድም  በአድማጭ  ፍለጎት አይለወጥም (“አይሁድ ምልክትን ይለምናሉ፤ የግሪክ ሰወችም ጥበብን ይሻሉ እኛ ግን የተሰቀለዉን ክርስቶስን እንሰብካለን…”) መስቀሉ  በሌላ የሰዉ  ጥበብ ሲተካም እግዚአብሔር ኃይሉን በመግለጥ አይተባበርም።

ስለሆነም  አሠራርን መመርመር ያስፈልጋል! በጌታ ስም የሚመጣ ሁሉ ሁልጊዜ የተባረከ አይደለም! የተሰቀለዉ ኢየሱስ መዐዛና መርህ የሌለበት አሠራር (የሠራ ቢመስልም እንኯ) እግዚአብሐር የለበትም። በሰዉ ጥበብ ላይ ተመስርቶ፣ ትርፍ አግብስባሽ ሆኖ፣ እኛን አገልጋዮች ከዋክብትና ትንንሽ አማልክት የሚያደርግ መንፈስ “የመጨረሻዉ” ምልክት እንጅ የወንጌል ምልክት ሊሆን አይችልም። ስለዚህ ጠቢብ የጌታችንንና የሐዋርያቱን ትምህርት በልቡ ያኖራል- “ተጠንቀቁ” (ኢየሱስ ክርስቶስ ማቴ 24፡4)

“ሁሉን ፈትኑ፣ መልካሙንም ያዙ” (ቅዱስ ጳዉሎስ 1ተሰ 5፡ 20)

 

Last modified onFriday, 10 April 2015 05:00
Mamusha Fenta

Mamusha Fenta is a Bible expositor and conference speaker residing in Addis Ababa, Ethiopia.

Website: www.mamushafenta.com/

11 comments

  • kiya
    kiya Tuesday, 21 April 2015 09:17 Comment Link

    I really am interested in reading your articles , they are more constructive for a mere Christian like me.I want to bless God for giving us such a responsible and a more reliable teacher.stay blessed

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:36 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:35 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:34 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:34 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:33 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:33 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:33 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:33 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

  • Elsa Araya
    Elsa Araya Tuesday, 21 April 2015 07:33 Comment Link

    *Mamusha! God bless you, man of God! And Praise the Lord that has anointed you!!!

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

Log in or Sign up