ቃል አቀባይነት

  • Read 4247 times
  • Print
  • Email

ሰሞኑን በነበረዉ የአሜሪካ የበጀት ክርክርና ቀዉስ ምክንያት በተደጋጋሚ መገናኛ ብዙሃን ብቅ ይሉ የነበሩ ዋና ሰዉ ጄይ ካርኔይ ይባላሉ። ሥራቸዉ የቤተ መንግሥት ቃል አቀባይነት (Whitehouse press secretary) ነዉ። ባጭሩ የፕሬዝዳንቱና የመንግሥታቸዉ “አፍ” (አፈ-ንጉሥ) ናቸዉ። ከዚህ የተነሳ ሲናገሩ ልብ ብላችሁ ከሆነ የሚያንጸባርቁት የራሳቸዉን ስሜትና አስተሳሰብ ሳይሆን የፕሬዝዳንቱን ነዉ። የሚናገሩት ተደጋጋሚ ሐረግ፡- “በፕሬዝዳንቱ እምነት”፤ “የፕሬዝዳንቱ አሳብ”  የምትል ናት። በዚያች “የንጉሥ መድረክ” ላይ የወደዱትን ሊሆኑ፣ የተሰማቸዉን ሊናገሩ አይችሉም። የቆሙት ንጉሥና መንግሥቱን ወክለዉ እንጂ የተሰማቸዉን ለመሆን አይደለምና።

የእኝህ ሰዉ ሥራ የእኔንና የብዙ አገልጋዮችን ጥሪ አስታወሰኝ። ጥሪያችን ልክ እንደሳቸዉ ነዉ፡- ንጉሡን እግዚአብሔር በመወከል የእርሱን አሳብና የመንግሥቱን አቋም ማንጸባረቅ ብቻ። “በእግዚአብሔር ፊት በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ባለዉ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት፤ በመገለጡና በመንግሥቱም እመክርሃለሁ ቃሉን ስበክ… (2ጢሞ 4፡1-2)። ስለሆነም የመሰለንን፣ ምኞታችንን፣ የአድማጭ ፍላጎትንና ለእኛ ከብር የሚያመጣን ነገር ሁሉ ልንናገር አልተፈቀደልንም። በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር አንዳንድ ነቢያትን “…ዉሸት…በስሜ ይናገራሉ…አላኳቸዉም፣ አላዘዝኳቸዉም አልተናገርኳቸዉም [ይልቁንም] የልባቸዉን ሽንገላ ይሰብኩላችኋል …” በማለት ይወቅሳል (ኤር 14፡14)። እንደዚህ ያሉ በንጉሡ ስም የራሳቸዉን ልብ የሚናገሩ ቃል አቀባዮች ታላቅ ቁጣና ፍርድ እንደሚጠብቃቸዉ ይናገራል (ቁ.15)። 

ቃል አቀባይነት እጅግ ክቡር ሥራ ነዉ! ንጉሥን ወክሎ ከመቆም የበለጠ ክቡር ሥራ ምን አለ? የንጉሡ እግዚአብሔር ሥልጣንና ኃይል አብሮን ይሆናል፣ ይሠራል! ነገር ግን ቃል አቀባይነት ደግሞ እጅግ የሚያስፈራ ሥራ ነዉ። የንጉሡን አሳብ (ቃሉን) በጥንቃቄ መረዳትና እርሱን ብቻ ለማንጸባረቅ መጨከን ያስፈልገናል። 

የንጉሥ አፍ የሆናችሁ ጓደኞቼ በዚህ የመጨረሻ ዘመን ንጉሡና መንግሥቱ እንዲከበሩ በምንቆምባቸዉ ቦታዎች ሁሉ አሳቡን እናገልግል። እዉነተኛ መንፈሳዊ ሥልጣን የሚመነጨዉ ንጉሡን በትክክል በመወከል እንጂ በራሳችን ጥበብ አይደለም። የሚመጡት የሳምንት መጨረሻ ቀናት፤ ከዚያም በኋላ እስኪመጣ ድረስ ይህን ለማድረግ የጨከነ መንፈስ ይስጠን። 

Mamusha Fenta

Mamusha Fenta is a Bible expositor and conference speaker residing in Addis Ababa, Ethiopia.

Website: www.mamushafenta.com/

5 comments

  • yonathan wondimu
    yonathan wondimu Thursday, 30 April 2015 16:08 Comment Link

    We are just called to be a tub for the water to flow be blessed.

  • yonathan wondimu
    yonathan wondimu Thursday, 30 April 2015 16:07 Comment Link

    We are just called to be a tub for the water to flow be blessed.

  • Tesfalem mamo
    Tesfalem mamo Tuesday, 28 April 2015 07:33 Comment Link

    It's not like I want You to be my mentor or anything because I already have one in my church but I never forget everything You say and belive. I alwys qout from your ideas when talking to people. I use your name a lot often to speak my mind about my belief specially about being satisfied in only being God child not anything else. So I am using this opportunity to say thanks and God is really using you in changing lots of life and in helping people run the race. That little boys two fish and five bread was enough for five thousand's... I am one of the thousands. God bless brother

  • Tesfalem mamo
    Tesfalem mamo Tuesday, 28 April 2015 07:28 Comment Link

    It's not like I want You to be my mentor or anything because I already have one in my church but I never forget everything You say and belive. I alwys qout from your ideas when talking to people. I use your name a lot often to speak my mind about my belief specially about being satisfied in only being God child not anything else. So I am using this opportunity to say thanks and God is really using you in changing lots of life and in helping people run the race. That little boys two fish and five bread was enough for five thousand's... I am one of the thousands. God bless brother

  • Tabor
    Tabor Sunday, 26 April 2015 20:22 Comment Link

    Dear Mamusha Fenta your blogs are very powerful and life changing . They have helped me to examine my Christian life as well as my calling. God bless you !!!

Leave a comment

Make sure you enter all the required information, indicated by an asterisk (*). HTML code is not allowed.

Log in or Sign up